EDGEን ይተዋወቁ!

በዲጂታል ዘመን የወደፊት ህልምዎን ያሳኩ። ተፈላጊ ክህሎቶችን ያዳብሩ፣ ከሃገር ውስጥ እንዲሁም ከውጭ አገር ድርጅቶች ጋር በመገናኘት እያደገ ባለው የኢትዮጵያ ጊግ (Gig) ኢኮኖሚ ውስጥ የስራ ፍላጎቶን ያሳኩ።

በጊግ ኢኮኖሚ የስራ እድሎችን ያግኙ
እንኳን ወደ EDGE ፕሮግራም በደህና መጡ

የEDGE ፕሮግራም የማስተርካርድ ፋውንዴሽን (MasterCard Foundation) ፕሮግራም ሲሆን ከአጋሮቹ ከሃይብሪድ ዲዛይንስ ኃ.የተ.የግ.ማ፣ Qua Qua Capitals፣ እና R&D Group ጋር እየተተገበረ ይገኛል።

የዚህ ፕሮግራም ዋነኛ ዓላማ ለ301,257 ወጣቶች (80% ወጣት ሴቶች፣ 20% ወጣት ወንዶች እና 10% ለተለያዩ ችግሮች የተጋለጡ ወጣቶች) በጊግ (Gig) ኢኮኖሚ የተሳካ የስራ እድል እንዲያገኙ ማገዝ ነው።
የፕሮግራሙ  ዋና ዋና ግቦች፡
  • ወጣቶች ወደ ጊግ ስራ (Gig Work ) ለመግባት የሚያስችላቸው ክህሎት ማሳደግ።
  • በአይቲ (IT) የታገዙ የጊግ ስራዎች (Gig Work) ምርቶችና አገልግሎቶች ማስፋት።
  • ኢትዮጵያ የጊግ ስራ (Gig Work) መዳረሻ እንድትሆን በአግባቡ ማስተዋወቅ።
  • የጊግ ስራ (Gig Work)  ዘርፉን የሚመሩ ፖሊሲዎችና ደንቦች እንዲዘጋጁ እና እንዲተገበሩ ማድረግ እንዲሁም በዘርፉ የተሰማሩ አካላት መካከል ያለው ቅንጅት ማጠናከር።

EDGE ወጣት ሴቶችን፣ የሃገር ውስጥ ተፈናቃይ  እና ስደተኛ ወጣቶችን እንዲሁም አካል ጉዳተኞችን የሚቀበልሁሉን አቀፍ ፕሮግራም ነው። ይህ ፕሮግራም ለወጣቶች  አስፈላጊ የዲጂታል ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ በማገዝ እንዲሁም የሥራ ዕድሎችን በማመቻቸት  የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ያስችላቸዋል።

አገልግሎቶቻችን

አሁን ይመዝገቡ እና ወደ ሥራ ዕድልዎ መንገድ ይጀምሩ

ማህበራዊ ገጾቻችን ይከተሉ​

አጋሮቻችን

ስለ ማስተርካርድ ፋውንዴሽን

ማስተርካርድ ፋውንዴሽን የካናዳ የበጎ አድራጎት ድርጅት የተመዘገበ እና በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ መሠረቶች አንዱ ነው። በአፍሪካ ውስጥ ያሉ ወጣቶች እና በካናዳ ውስጥ ያሉ ተወላጆች ክብር ያለው እና አርኪ ስራ እንዲያገኙ ለማስቻል የትምህርት እና የፋይናንስ ማካተትን ለማሳደግ ከራዕይ ድርጅቶች ጋር ይሰራል። የወጣት አፍሪካ ስራዎች ስትራቴጂው በ2030 30 ሚሊዮን ወጣቶች የተከበረ እና አርኪ ስራ እንዲያገኙ ለማስቻል ያለመ ሲሆን የኤሌቪ ስትራቴጂው በካናዳ የሚገኙ 100,000 ተወላጆች ትምህርታቸውን እንዲያጠናቅቁ እና ከባህላቸው፣ እሴታቸው እና ምኞታቸው ጋር ወደታሰበ ትርጉም ያለው ስራ እንዲሸጋገሩ ያደርጋል።

በ 2006 የተቋቋመው በማስተርካርድ ልግስና የህዝብ ኩባንያ ሲሆን ፋውንዴሽኑ ራሱን የቻለ ድርጅት ነው። የእሱ ፖሊሲዎች፣ ተግባራት እና የፕሮግራም ውሳኔዎች የሚወሰኑት በዳይሬክተሮች ቦርድ እና በአመራር ቡድን ነው። ስለ ፋውንዴሽኑ ተጨማሪ መረጃ፣ እባክዎን www.mastercardfdn.orgን ይጎብኙ።

Mastercard Foundation Logo

አሁን ይመዝገቡ እና ወደ ሥራ ዕድልዎ መንገድ ይጀምሩ

ማህበራዊ ገጾቻችን ይከተሉ​

በተደጋጋሚ የሚጠየቁ ጥያቄዎች

EDGE (ኢንተርፕረነርሺፕ በዲጂታል እና ጊግ ኢኮኖሚ) ወጣቶችን በተለይም ሴቶችን በዲጂታል የውጪ አቅርቦት እና ነፃ አውጭ ኢኮኖሚ ውስጥ ስኬታማ ለመሆን የሚያስፈልጉ ክህሎቶችን ፣ መሳሪያዎችን እና እድሎችን የሚያስታውቅ ሀገራዊ ተነሳሽነት ነው።

የሚከተሉትን ካሟሉ  ማመልከት ይችላሉ:

  • እድሜያቸው ከ15-35 የሆኑ ናቸው።
  • ሥራ የሌላቸው ወይም በቂ የገቢ ምንጭ የሌላቸው
  • መሰረታዊ የዲጂታል ዕውቀት ያላቸው ወይም ለመሰልጠን ፈቃደኝነት ያላቸው
  • ስልጠናውን ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ የሆኑ
    ፕሮግራሙ ቅድሚያ የሚሰጠው ለወጣት ሴቶች፣ ለሃገር ውስጥ ተፈናቃይ እና ስደተኛ ወጣቶች እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች ነው።

ተሳታፊዎች የ EDGE ፕሮግራምን ያለምንም ክፍያ መቀላቀል ይችላሉ። ሆኖም የሥራ ዕድል ለማግኘት ተሳታፊዎች ስልጠናውን በአግባቡ ማጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል።

በዚህ ፕሮግራም ውስጥ የሚያገኙት የስልጠና አይነቶች፡-

የዲጂታል ክህሎት
የህይወት ክህሎት ስልጠና (ተግባቦት, ሙያዊነት, የጊዜ አጠቃቀም)
ሙያዊ ክህሎት (ቨርቹዋል አሲስታንት፣ ኮንቴንት ማዘጋጀት፣ ግራፊክ ዲዛይን)

እንደየ ስልጠናው አይነት ከ 4 እስከ 8 ሳምንታት ሊፈጅ ይችላል። ከስልጠና በኋላ የስራ ዕድሎች የሚመቻቹ ይሆናል።

አዎ። በሚከተሉት መልኩ ልንደግፎት እንችላለን ፡-

  • የፍሪላንስፕሮፋይሎን መገንባት
  • በኦንላይን የጊግ ስራዎችን  እና ደንበኞችን እንዲያገኙ ማስቻል
  • የውጭ የስራ እድሎችን ከሚያመቻቹ ድርግጅቶች ጋር ማገናኘት
  • በአከባቢዎ ወይም በርቀት የስራ እድሎች እንዲሳተፉ ማድረግ

እንደሚመርጡት የስራ ዘርፍ ኮምፒውተር/ስማርት ስልክ እና ኢንተርኔት ቢኖሮት ይመረጣል። ይሁን እንጂ የ EDGE ማዕከሎች እና በየአካባቢው ያሉ የአጋር ተቋማት ማእከላት ውስጥ የኮምፒውተር እና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በነጻ ማግኘት ይችላሉ።

EDGEን በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ከተሞች እና በዙሪያቸው ባሉ አካባቢዎች እየሰራ ይገኛል።  በበለጠ የመዳረሻ ቦታዎችን ለማወቅ የማመልከቻ የመተግበሪያውን ገጽን ይመልከቱ።

‘’አሁኑኑ ያመልክቱ” የሚለውንየማመልከቻ ገጽ በመጎብኝት፣ የምዝገባ ቅጹን በአግባቡ በመሙላት ማመከት ይችላሉ።  አስፈላጊውን መስፈርት ላሟሉ አመልካቾች ጥሪ የሚደረግ ይሆናል።

አሁን ይመዝገቡ እና ወደ ሥራ ዕድልዎ መንገድ ይጀምሩ​

ማህበራዊ ገጾቻችን ይከተሉ

የእርስዎ ደህንነት ቅድሚያ ይሰጠዋል

በ EDGE ፕሮግራም፣ እያንዳንዱ ወጣት ደህንነቱ የተጠበቀና ክብሩን የሚጠብቅ የሥራ ከባቢ ሊኖረው እንደሚገባ እናምናለን። በኦንላይም ሆነ በአካል ለሚፈጸም ማንኛውም ዓይነት ጥቃት፣ ብዝበዛ ወይም ክብራችሁን ለሚነካ ድርጊት ፈጽሞ ትዕግስት የለንም። ትክክል ያልሆነ ነገር ሲያጋጥም ድምፃችሁን አሰሙ። የርቀት ሥራ ማለት ከአደጋ መራቅ ማለት አይደለም፤ ደህንነታችሁ መብታችሁ ነው። ሁሌም ንቁ ሁኑ፣ የውስጥ ስሜታችሁን እመኑ፣ እና የማይመች ሁኔታ ሲያጋጥማችሁ ወዲያውኑ አሳውቁን። ስጋታችሁን በቀጥታ እና ማንነታችሁን ሳትገልጹ በ safe@edge.et ላይ ሪፖርት ማድረግ ትችላላችሁ። ክብር ያለው ሥራ ደህንነቱ የተጠበቀ ነው። መብታችሁን ለማስከበር፣ ድምፃችሁን ለመደገፍ እና ጥፋተኛ አካላት ተጠያቂ ለማድረግ ከጎናችሁ ነን። የእናንተ ደህንነት የማይደራደርበት ጉዳይ ሲሆን ለስኬታችሁም መሰረት ነው።